በጃፓን ቶኪዮ የግማሽ ማራቶን አትሌት ሰለሞን ባረጋ አሸነፈ።
######################
በጃፓን ቶኪዮ በተካሄደው የግማሽ ማራቶን ውድድር አትሌት ሰለሞን ባረጋ አሸንፈዋል ።
አትሌት ሰለሞን ርቀቱን ለማጠናቀቅ 1:01.21 ወስዶበታል።
በሴቶች ምድብ አትሌት መስከረም ማም ሦስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።
በሌላ ዜና በአምስተርዳም ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች አሸንፈዋል ።
በሴቶች ውድድር አትሌት አይናለም ደስታ በ2 :17.37 በመግባት የግል ምርጥ ሰዓቷን አስመዝግባ አሸንፋለች።
አትሌት ብርቱካን ወልዴ 2ኛ ደረጃን ይዛ ስታጠናቅቅ አትሌት መቅደስ ሽመለስ 3ኛ ደረጃን ይዛ ፈፅማለች ።
በወንዶች የባለፈው ዓመት አሸናፊ አትሌት ጸጋዬ ጌታቸው 2ኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል፡፡
አትሌት ጌታነህ ሞላ 3ኛ ደረጃን ይዞ ውድድሩን ጨርሰዋል ።
የኬንያዊውን አትሌት ጂዮፍሪ ኪብቹምባ ውድድሩን በአንደኝነት አጠናቋል፡፡