በሳምንቱ መጨረሻ ላይ በተካሄዱ የጎዳና ላይ ውድድሮች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ተቀዳጅቷል ።
በሕንድ ኮልኮታ የታታ ስቲል የ25 ኪሎሜትር ውድድር አትሌት ደጊቱ አዝመራው አሸንፋለች ።
አትሌቷ እርቀቱ ለማጠናቀቅ 1:19:36 የወሰደባት ሲሆን፣አትሌት ሱቱሜ አሰፋ ሁለተኛ ፤አትሌት መሰለች አለማየሁ ሶስተኛ በመሆን አሸንፈዋል ።
በውድድሩ ላይ የተሳተፉት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አትሌት ኩፍቱ ጣሂር ፤ አትሌት ዘመኗ ደምለው እና አትሌት ነፃነት ታፈረ ከአራት እስከ ስድስት ያለውን ደረጃ በመያዝ ውድድራቸውን አጠናቀዋል።
አትሌት ጋዲሴ ደምሴ የታይፔ ማራቶንን በ2:24:17 የቦታውን ክብረወሰን በማሻሻል አሸንፋለች ።
ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ትርፌ በየነ በ2:24:19 በመግባት ሁለተኛ ወጥታለች።
በሌላ በኩል በጓንግዙ ማራቶን አትሌት አፈወርቅ መስፍን በቀዳሚነት አሸንፏል ።
አትሌት አፈወርቅ እርቀቱን ለማጠናቀቅ 2:12:23 ወስዶበታል።
በሴቶች አትሌት ቤተልሔም አፈንጉስ በ2፡27.52 ሁለተኛ ስትወጣ አትሌት ጫልቱ ጭምዴሳ በ2፡31.37 ሦስተኛው ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።




