አትሌት ሃዊ ፈይሳ የቺካጎ ማራቶን አሸነፈች

########################

ጥቅምት 02/2018 ዓ.ም

አትሌት ሃዊ ፈይሳ 47ኛውን የቺካጎ ማራቶን አሸነፈች።

አትሌት ሃዊ ርቀቱን ለማጠናቀቅ 2:14.56 ሰዓት ወስዶባታል ።

ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊ አትሌት መገርቱ አለሙ በ2:17:18 በመግባት 2ኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች።

በወንዶች ኢትዮጵያዊያኑ አትሌቶች አትሌት ሁሰዲን መሀመድ እና አትሌት ሰይፉ ቱራ 5ኛ እና 6ኛ ደረጃን በቅደም ተከተል ይዘዋል ።

ኡጋንዳዊው አትሌት ጃኮብ ኪፕሊሞ በ2:02:23 አሸንፏል።

ኬንያውያኑ አሞስ ኪፕሩቶ እና አሌክስ ማሳይ ሁለተኛና ሦስተኛ ሆነው ውድድሩን ፈፅመዋል።

Categories: Uncategorized