ለ13ኛው የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች እና 4ኛው የኢትዮጵያ ከ18 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና በድምቀት ለማካሄድ ቅድመ ዝግጅት ተጠናቀቀ

ግንቦት 14/2017 ዓ.ም

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በድሬዳዋ ከተማ የ13ኛው የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች እና 4ኛው የኢትዮጵያ ከ18 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከግንቦት 18-24/2017 ዓ.ም ለማካሄድ ዝግጅቱን አጠናቋል ፡፡

በሻምፒዮናው ላይ 8 ክልሎች ፣ 2 ከተማ አስተዳደሮች እና 35 ክለቦች እና ተቋማት በውድድሩ ላይ የሚካፈሉ ሲሆን ሻምፒዮናም በሁለት የእድሜ ምድብ ይካሄዳል ።

ከ20 ዓመት በታች 359 ሴቶች 463 ወንዶች በድምሩ 825 አትሌቶች እንዲሁም ከ18 ዓመት በታች 178 ሴቶች 192 ወንዶች በድምር 370 በሁለቱም የእድሜ ምድብ በአጠቃላይ 1,195 አትሌቶች እንደሚወዳደሩ በጋዜጣዊ መግለጫው ተጠቁመዋል ።

የሻምፒዮናው አላማም እ.ኤ.አ ከጁላይ 16-20/2025 በናይጄሪያ አቡኩታ ከተማ ለሚካሄደው የአፍሪካ ከ18 ዓመት እና ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶችን ለመምረጥ እንደሆነ ተነስቷል ።

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን ፣የፌዴሬሽኑ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዮሐንስ እንግዳ፣ የፌዴሬሽኑ ውድድር እና ተሳትፎ ዳይሬክተር አቶ አስፋው ዳኜ ፣ የፌዴሬሽኑ የኮሚኒኬሽን ከፍተኛ ባለሙያ አቶ መሐሪ ነጋሽ እና የፌዴሬሽኑ የህክምና ከፍተኛ ባሉሙያ ወይዘሮ ቅድስት ታደሰ በጋራ በመሆን በሻምፒዮናው ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

Loading

Categories: Uncategorized