የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለቦሬ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል የስፖርት ትጥቅ ድጋፍ አደረገ ።

መጋቢት 07/2017 ዓ.ም

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለቦሬ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል የስፖርት ትጥቅ ድጋፍ አድርጓል ።

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ባለሙያዎች አቶ ይሄይስ ግርማ እና አቶ ዳንኤል ኪዳኔ በጋራ በመሆን ሰልጣኞች እና አሰልጣኞች በተገኙበት የስፖርት ትጥቁን አስረክበዋል ።

የቦሬ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል አመራሮች እና አሰልጣኞች ፌዴሬሽኑ ላደረገላቸው ድጋፍ በማመስገን የስፖርት ትጥቁን ተረክቧል ።

ፌዴሬሽኑ ለቦቆጂ ፣ ለደብረብርሃን እና ለሀገረሰላም አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከላት ዓመታዊ የስፖርት ትጥቅ ማድረጉ የሚታወስ ነው።

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የስፖርት ትጥቅ ስርጭቱን አሁንም አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ።

Categories: Uncategorized