መረጃ !

ለክልሎች ፣ከተማ አስተዳደሮች፣ክለቦችና ተቋማት :-

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን 43ኛው ጃንሜዳ ኢንተርናሽናል ሀገር አቋራጭ ውድድር በልዩ እና ታላቅ ድምቀት ለማካሄድ ከፍተኛ ዝግጅት በማድረግ ላይ ይገኛል።

ውድድሩ የሚካሄድበት ቀን ህዳር 07/2018 ዓ.ም እንደነበር ይታወቃል ።

ሆኖም ግን በአሜሪካ ፍሎሪዳ የሚካሄደው 46ኛው የዓለም አገር አቋራጭ ሻምፒዮና ቀን መቅረብና ለቪዛ ፕሮሰስ በቂ ጊዜ በማስፈለጉ ምክንያት ሻምፒዮናው ወደ ጥቅምት 30/2018 ዓ.ም መቀየሩን እያሳወቅን ከወዲሁ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እንገልፃለን ።