በግላስጎ በተካሄደው የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተካፍሎ በድል ለተመለሰው ብሔራዊ ቡድናችን አቀባበል ተደረገለት፤

የካቲት 26/2016 ዓ.ም ከማርች 1-3/2024 በእንግሊዝ ግላስጎ በተካሄደው 19ኛው የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ተካፍሎ በድል ለተመለሰው የልኡካን ቡድን ዛሬ ቀን ላይ አዲስ አበባ ቦሌ ኢንተርናሽናል አየር ማረፊያ ሲደርስ … Read More

በ19ኛው የአለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ከአፍሪካ አንደኛ ከዓለም አምስተኛ በመሆን አጠናቃለች።

ከማርች 1-3/2024 በእንግሊዝ ግላስጎ ሲካሄድ በነበረው የ19ኛው የዓለም የቤት ዉስጥ ሻምፒዮና ከ130 በላይ አገሮች የተውጣጡ ከ650 በላይ አትሌቶቸ በዚህ ሻምፒዮና ተሳትፈውበታል ። ኢትዮጵያ በ800 ሜትር፣ በ1500 ሜትር እና በ3000 ሜትር … Read More

በ19ኛው የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና የሚካፈለውን የልዑካን ቡድናችን ወደ እንግሊዝ ግላስጎ ተሸኘ፤

ከማርች 1-3/2024 በእንግሊዝ ግላስኮ በሚካሄደው 19ኛው የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ሃገራችንን የሚወክለው ብሔራዊ ቡድናችን እኩለ ቀን ላይ አዲስ አበባ ቦሌ ኤርፖርት በመገኘት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ክብርት ረዳት … Read More

የ6ኛው የአፍሪካ የአገር አቋራጭ ሻምፒዮና የልዑካን ቡድን በሰላም ወደ አገራቸው ገብተዋል ።

የልዑካን ቡድኑ ከሌሊቱ 7:00 አዲስ አበባ ቦሌ አለም አቀፍ ኤርፖርት ሲደርሱ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት ዘርፍ ሚ/ር ዴኤታ አምባሳደር መስፍን ቸርነት አና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ክብርት ረ/ኮሚሽነር … Read More

ክብርት ረ/ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ የኢ.አ.ፌ ፕሬዝዳንት የዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና አትሌቶች በመጨረሻው ልምምዳቸው ላይ ተገኝተው አበረታቱ።

የ19ኛውን የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና የሚካፍሉ አትሌቶቻችን ዛሬ የካቲት 18/2016ዓ.ም በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ከማለዳው 12:30 የመጨረሻውን ልምምዳቸውን አድርገዋል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ክብርት ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ በቦታው በመገኘት … Read More

በ6ኛው የአፍሪካ አገር አቋራጭ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ በሁለተኝነት የሚዳሊያ ሰንጠረዥ በመያዝ አጠናቃለች

በዛሬው እለት የካቲት 17/2016 በቱኒዝያ ሃማመት በተደረገው 6ኛው የአፍሪካ አገር አቋራጭ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትያጵያን ጨምሮ አስራ አንድ ሃገራት የተካፈሉ ሲሆን ኢትዮጵያ ወጣት ሴት 6 ኪ.ሜ.፣ በወጣት ወንድ 8 ኪ.ሜ.፣ በአዋቂ … Read More

በዛሬው የሽኝት መርሃ ግብር የ19ኛው የዓለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ሻምፒዮና እና የ6ኛው የአፍሪካ የአገር አቋራጭ ሻምፒዮና የልዑካን ቡድን የተሸኙ ሲሆን :-

በሽኝት መርሃግብሩ ላይ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ክብርት ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ የሚከተለውን መልእክት አስተላልፈዋል ” ሁላችሁም በመተጋገዝ፣ ለጋራ ድል በአንድነት ሃገርችንን የምትወክሉ አትሌቶቻችን የምንወዳትን የአገራችንን ሰንደቅ ዓላማ በዓለም አደባባይ … Read More

በቱንዚያ ቱኒዝ ለሚደረገው ለ6ኛው የአፍሪካ የአገር አቋራጭ ውድድር ዝግጅቱ ተጀምሯል ። ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ለአራት አመታት ተቋርጦ የነበረው እና በConfederation of Africam Athletics (CAA) የሚዘጋጀው የአፍሪካ የአገር አቋራጭ ውድድር ዘንድሮ ለ6ኛ ጊዜ … Read More

የጃፓን የካሳማ ከተማ ከንቲባ ለኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የተለያዩ የስፖርት ቁሳቁሶች ድጋፍ አደረጉ ።

ጥር 30/2016 ዓ.ም ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ በጃፓን አገር ካሳማ ከተማ ላለፋት ተከታታይ አምስት አመታት በዲሴምበር ወር በጀግናው አትሌት ሻምበል አበበ በቂላ ለመዘከር የግማሽ ማራቶን ውድድር የሚዘጋጅ ሲሆን የውድድሩ አዘጋጅ የካሳማ ከተማ ከንቲባ … Read More

53ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ስፖርት ክለብ የበላይነት ተጠናቀቀ ፤

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ አንጋፋውና በርካታ አትሌቶችን ያፈራውን ዘንድሮ ለ53ኛ ጊዜ ከጥር 21-26/2016 በአዲስ አበባ ከተማ ኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ የተካሄደው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከ1100 በላይ አትሌቶች ክልላቸውን፣ ክለባቸውንና ተቋማቸውን ወክለው የተሳተፋበት እና ጠንካራ … Read More