የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን ዓድዋ ከተማ ገቡ::

የካቲት 21/2017 ዓ.ም

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን 20ኛው የኢትዮጵያ ማራቶን ሪሌ ውድድር ላይ ለመሳተፍ ዓድዋ ከተማ ገብተዋል ።

ፕሬዚዳንቱ አክሱም አፄ ዮሐንስ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል ።

የዓድዋ ከተማ ከንቲባ አቶ ተስፋይ ገብረውልድ እና ሌሎች የከተማ አመራሮች አቀባበል አድርጎላቸዋል ።

ከፕሬዚዳንቱ በተጨማሪ የፌዴሬሽኑ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ፣የማኔጅመንት አባላት እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ዓድዋ ከተማ ገብተዋል ።

+

Categories: Uncategorized