ተጠባቂው የቶከዮ ማራቶን በኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸናፊነት ተጠናቀቀ ።

የካቲት 23/2017 ዓ.ም

የቶከዮ ማራቶን በሁለቱም ጾታ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በበላይነት አሸንፈዋል።

በወንዶች ታደሰ ታከለ ሲያሸንፍ በሴቶች ደግሞ አትሌት ሱቱሜ አሰፋ በበላይነት አሸንፋለች ።

በአለም አትሌቲክስ የፕላቲኒየም ደረጃ በተሰጠው ማራቶን በሴቶች አትሌት ሱቱሜ አሰፋ 2:16. 31 በመግባት በአንደኝነት አሸንፋለች ።

በወንዶች የቶክዮ ማራቶን አትሌት ታደሰ ታከለ በ2:03.23 በመግባት የግል ምርጥ ሰአቱን ጭምር በማሻሻል አሸንፈዋል ።

አትሌት ደረሳ ገለታ በ2 :03.51 በመግባት ሁለተኛ ደረጃ ይዞ አጠናቀዋል ።

Categories: Uncategorized