በስሎቬኒያ ሉቡሊያና ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ፆታ ድል ተቀዳጅቷል

########################

ጥቅምት 9/2018 ዓ.ም

በሱሎቬኒያ ሉቡሊያና ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ፆታ ድል ተቀዳጅቷል ።

በወንዶች ውድድር አትሌት ሃፍታሙ አባዲ በ2:06:52 በመግባት በቀዳሚነት አጠናቋል።

በውድድሩ ላይ የተሳተፈው ኢትዮጵያዊ አትሌት ከማል ሁሴን ሦስተኛ ወጥቷል።

በሴቶች አትሌት ትግስት ገዛኸኝ በ2:22:46 በመግባት በአንደኝነት አሸንፋለች።

Categories: Uncategorized