በሳምንቱ መጨረሻ በተደረጉ የጎዳና ላይ ሩጫዎች ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች አሸንፈዋል።

የካቲት 30/2018 ዓ.ም

በሊዝበን ግማሽ ማራቶን አትሌት ፅጌ ገብረሰላማ ለተከታታይ ሁለተኛ ዓመት አሸንፋለች ።

አትሌት ፅጌ ርቀቱን ለማጠናቀቅ 1:04.48 ወስዶባታል።

አትሌት ግርማዊት ገ/እግዚአብሔር በ1:07.30 5ኛ ወጥታለች።

በፈረንሳይ ዴ ሁካ ሰሚ ደ ፓሪስ የግማሽ ማራቶን አትሌት ፍታው ዘርኣይ በቀዳሚነት ውድድራን ፈፅማለች ።

አትሌቷ የገባችበት 1:05.12 የቦታው ምርጥ ሰዓት ነው።

ጃፓን ናጎያ ሴቶች ማራቶን አትሌት አይናለም ደስታ 3ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።

በአምስት ወር ውስጥ ሁለተኛ ማራቶኗን የተካፈለችው አትሌት አይናለም ውድድሩን ለማጠናቀቅ 2:22:37 ሰዓት ወስዶባታል፡፡

Categories: Uncategorized