የአዲዳስ ካምፓኒ ማርኬቲንግ ማኔጅመንት ተወካይ ዳኒኤል ሎቤ በአዲስአበባ

#############################

የካቲት 6/2018 ዓ.ም

የአዲዳስ ካምፓኒ የሩጫ ማርኬቲንግ ማኔጅመንት ተወካይ ዳኒኤል ሎቤ ዛሬ ጠዋት አዲስ አበባ ገብተዋል።

በዓለም አትሌቲክስ እውቅና ያገኘው የአደይ አበባ ዓለም አቀፍ የመለማመጃ ትራክ ፣ በመገባደድ ላይ የሚገኘውን ስቴዲየም እና የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ጎብኝተዋል።

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጽ/ቤት ሀላፊ ዶክተር አመንሲሳ ከበደ ቦሌ አለምአቀፍ አየር ማረፊያ አቀባበል ያደረጉላቸው ሲሆን፣ በጉብኝታቸው ላይ ማብራሪያ አድርጎላቸዋል ።

ጉብኝታቸው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የጀመረውን ዓለምአቀፍ የአትሌቲክስ ስፖርት ዲፕሎማሲ ግንኙነት የሚያጠናክር እንደሆነ ተመላክቷል።

የዓለም አትሌቲክስ የውደድር ዋና ዳይሬክተር ፒርስ ኦክሎጋን በአዲስአበባ የነበራቸው ቆይታ ፣ውጤታማ እንደነበር የሚታወስ ነው።

Categories: Uncategorized