የዓለም አትሌቲክስ አንደኛ ደረጃ ዳኝነት ስልጠና ተጠናክሮ ቀጥሏል።

##################################################

ጥር 15/2017 ዓ.ም

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የዓለም አትሌቲክስ አንደኛ ደረጃ ዳኝነት ስልጠና በአዲስአበባ ስፖርት ስልጠና ማዕከል እየሰጠው የሚገኝ ስልጠና አጠናክሮ ቀጥሏል።

ሁለተኛ ቀኑን የያዘው የዓለም አትሌቲክስ አንደኛ ደረጃ ዳኝነት ስልጠና በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ቀጥሎ ውለዋል ።

ስልጠናው ላይ ከሁሉም ክልሎች እና ከተማ አስተዳድሮች የተወጣጡ ሰልጣኞች እየተሳተፉ የሚገኙ ሲሆን፣ስልጠናው በኢትዮጵያዊ ኢንተርናሽናል ኢንስትራክተር ሽመልስ ዳዊት እየተሰጠ ይገኛል።

ስልጠናው እስከ ጥር 18/2017 ዓ.ም የሚቀጥል መሆኑን የወጣው መርሀግብር ያመላክታል::

Categories: Uncategorized