-
ሎሬት ኮሎ/አትሌት ደራርቱ ቱሉፕሬዝዳንት
-
አትሌት ገብረእግኢአብሔር ገብረማርያምምክትል ፕሬዝዳንት
-
ዶ/ር ጋልዋክ ሮንጃልአባል
-
ዶ/ር በዛብህ ወልዴአቃቤ ንዋይ
-
አቶ በላይነህ ክንዴአባል
-
አቶ ፈሪድ መሃመድአባል
-
አቶ አድማሱ ሳጂአባል
-
ወ/ሮ ፎዚያ ኢድሪስአባል
-
አትሌት መሰረት ደፋርአባል
-
አቶ ቢልልኝ መቆያየፅህፈት ቤት ኃላፊ እንዲሁም የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል

ሎሬት ኮሎ/አትሌት ደራርቱ ቱሉ
ፕሬዝዳንት
- ሁለት ጊዜ የኦሎምፒክ ሻምፒዮና
- አንድ ጊዜ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና
- ሁለት ጊዜ የአገር አቋራጭ ሻምፒዮና
- ሁለት ጊዜ የአህጉራት ዋንጫ ሻምፒዮና
- አንድ ጊዜ የዓለም ወጣቶች አትሌቲክስ ሻምፒዮና
- ሁለት ጊዜ የአፍሪካ አትሌቲክሰ ሻምፒዮና

አትሌት ገብረእግኢአብሔር ገብረማርያም
ምክትል ፕሬዝዳንት
- የአለም አገር አቋራጭ ሻምፒዮና አምስት ጊዜ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት
- የአለም አገር አቋራጭ ሻምፒዮና ስድስት ጊዜ የብር ሜዳሊያ ባለቤት
- የአለም አገር አቋራጭ ሻምፒዮና ሶስት ጊዜ የነሃስ ሜዳሊያ ባለቤት
- የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ም/ፕሬዝዳንት (ከ2009 ጀምሮ)
- የአትሌቶች ተወካይ በመሆን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ስራ አስፈፃሚ (2003-2007)
- የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የስፖርት ክለብ የቦርድ አባል (ከ2004-2008)
- የኢትዮ ካርል አትሌቲክስ ክለብ ፕሬዚደንት (ከ2006-2007)

ዶ/ር ጋልዋክ ሮንጃል
አባል
- በጋምቤላ ክልል የቦክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንትነት ሆነው አገልግለዋል
- የጋምቤላ ክልል የስፖርት ምክር ቤት ም/ሰብሳቢ በመሆን አገልግለዋል

ዶ/ር በዛብህ ወልዴ
አቃቤ ንዋይ
- የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ዋና ፀሃፊ በመሆን ለሰባት አመታት አገልግለዋል
- የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዋና ፀሃፊ በመሆን ለሰባት አመታት አገልግለዋል
- የአፍሪካ ኦሎምፒክ ኮሚቴ አባል ሆነው አገልግለዋል
- የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ሊቀመንበር በመሆን አገልግለዋል
- በአትሌቲክሱ ዘርፍ የተለያዩ ጥናታዊ ፅሁፎች አበርክተዋል

አቶ በላይነህ ክንዴ
አባል
- የኢትዮጵያ ሆቴል አትሌቲክስ ክለብ ባለቤት (ሰከላ ወረዳ)
- በተለያዩ ጊዜያት ብሄራዊ የአትሌቲክስና የእግርኳስ ቡድኖችን ስፖንሰር አድርገዋል
- የባህርዳና የወለጋ ስቴዲየም እንዲገነባ የገንዘብ ድጋፍ አድርገዋል
- የትምህርና የጤና ተቋማትን በመገንባትና ሲገነቡ ድጋፍ በማድረግ እንዲሁም ሌሎች ሃላፊነቶችን በመወጣት ላይ ናቸው

አቶ ፈሪድ መሃመድ
አባል
- የሃረር ሲቲ እግር ኳስ ክለብ ም/ፕሬዝዳንት በመሆን እያገለገሉ ይገኛሉ
- የመረብ ኳስ ፌዴሬሽን ም/ፕሬዝዳንት (2000 – 2004 እ.ኤ.አ)
- የቼዝ ፌዴሬሽን ም/ፕሬዝዳንት (2009 – 2014 እ.ኤ.አ)

አቶ አድማሱ ሳጂ
አባል
- የአትሌቲክስ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝነት (2001-2008)
- የኢትዮጵያ አትሌቲክስ አሰልጣኞች ማህበር ፕሬዚዳንት በመሆን አገልግለዋል
- በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የቴክኒክ ኮሚቴ አባል (1997-2002)
- ለብዙ አመታት በኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ አትሌቲክስና የአትሌቲክስ አሰልጣኝነት ኮርሶችን በማሰተማር በተጨማሪም የጥናትና ምርምር ስራዎችን አካሄደዋል

ወ/ሮ ፎዚያ ኢድሪስ
አባል
- የትምህርት ደረጃ፡- የመጀመሪያ ዲግሪ
- በጋዜጠኝነት የ7 ዓመት የስራ ልምድ
- በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በአፋርኛ ቋንቋ የስፖርትና የመዝናኛ ዘርፍ ፕሮግራም አዘጋጅና ቡድን መሪ በመሆን በማገልገል ላይ ያሉ

አትሌት መሰረት ደፋር
አባል
- በ5000ሜ ሁለት ጊዜ የኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት
- በ5000ሜ ሁለት ጊዜ የአለም ሻምፒዮና የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት
- በ3000ሜ በአለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና አራት ጊዜ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት
- ከ2003-2007 የኢትዮጵያ አትሌቶች ተወካይ በመሆን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል
- ከ2007 ጀምሮ የኢትዮጵያ አትሌቶች ማህበር ም/ፕሬዝዳንት

አቶ ቢልልኝ መቆያ
የፅህፈት ቤት ኃላፊ እንዲሁም የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል
- በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጽ/ቤት ኃላፊነት (ከጥር 2005 እስከ አሁን)
- በአማራ ክልል ስፖርት ኮሚሽን በም/ኮሚሽነር (ከ2003 – 2005)
- በክልሉ ስፖርት ኮሚሽን የስፖርት ዘርፍ ኃላፊ (ከ1999 – 2000)
- በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ስፖርት ቢሮ የስፖርት ቡድን መሪ (ከ1997 – 1999)
- በተለያዩ ት/ቤቶች በርዕሰ መምህርነት፣ በአስተባባሪነት፣ በክፍለ ትምህርት መሪነትና በስፖርት ሳይንስ መምህርነት ለበርካታ አመታት አገልግለዋል